ዓለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች (ሲፒጄ)፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለስልጣናት የሸገር ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጋዜጠኞች ትዕግስት ዘሪሁንና ምንታምር ጸጋውን “ያለምንም ቅድመ ሁኔታ” ከእስር እንዲፈቱ ጠይቋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለስልጣን፣ ጣቢያው በጤና ባለሙያዎች ዙሪያ የሠራው ዘገባ “ግጭት ቀስቃሽ” እና “አድሏዊ” ነው በማለት ጣቢያው ዘገባውን እንዲያነሳ በደብዳቤ ማዘዙን ሲፒጄ ጠቁሟል፡፡
ፌደራል ፖሊስ ወደ ጣቢያው በመግባት የዜና ክፍል ሃላፊውን እሸቴ አሠፋን ጭምር ካሠረ በኋላ የዕለቱ’ለት እንደለቀቀው መስማቱንም ተቋሙ ጠቅሷል።
ሁለቱ ጋዜጠኞች ጳጉሜ 3 ፍርድ ቤት ይቀርባሉ የተባሉ ሲሆን፤ ሲፒጄ “ያለምንም ቅድመ ሁኔታ” ከእስር እንዲፈቱ መንግሥትን ጠይቋል።
