የአውሮፓ ህብረት ለአፍሪካ የ58.4 ቢሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ሊያደርግ ነው

Date:

የአውሮፓ ህብረት ለ2028-2034 ባለው ጊዜ ውስጥ ለውጭ ሀገራት ተግባራት ከተመደበው ጠቅላላ በጀት ውስጥ ትልቁን ድርሻ ለአፍሪካ ለመስጠት ማቀዱን አስታውቋል።

የቀረበው ረቂቅ በጀት እንደሚያሳየው፣ አፍሪካ 58.4 ቢሊዮን ዩሮ (68.35 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር) የገንዘብ ድጋፍ ልታገኝ ነው።

ይህ የገንዘብ ድጋፍ የህብረቱን የውጭ ጉዳይ የገንዘብ ድጋፍ ወደ አንድ ነጠላ መሣሪያ ለማዋሃድ በታቀደው “ግሎባል አውሮፓ” (Global Europe) በሚባለው አዲስ ፕሮግራም በኩል የሚሰጥ ነው።

የአውሮፓ ህብረት የገንዘብ ድጋፉን በዋናነት ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ እና የአካባቢ ኢኮኖሚን ለማሳደግ እንደሚጠቀምበት ገልጿል። ይህም ከኢኮኖሚ ውድቀት እና ሥራ አጥነት የሚመነጨውን ሕገወጥ ስደት ለመቀነስ ያለመ መሆኑን ቅዳሜ ገበያ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል ።

KGEthiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...