በየዓመቱ ከ9 ሺህ 500 በላይ ሰዎች በኤች አይ ቪ ይሞታሉ

Date:

በአዲስ አበባ፣ ጋምቤላ እና ሐረሪ ከፍተኛ የኤች አይ ቪ ስርጭት ባለባቸው ክልሎች ቀዳሚውን ስፍራ ይዘዋል ነው የተባለው።

መረጃው የወጣው በኤች አይ ቪ እና ቲቢ በሽታዎች ላይ በሚሰራው ኤድስ ሄልዝኬር ፋውንዴሽን ነው።

በየዓመቱ ወደ 8 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች በቫይረሱ እንደሚያዙ ተቋሙ ገልጿል።

በአጠቃላይ ከ600 ሺህ በላይ ሰዎች ከቫይረሱ ጋር ሲኖሩ ከእነዚህ ውስጥ 64 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው ተብሏል።

ምንም እንኳን በ2010 ዓ.ም ከነበረው 1 ነጥብ 6 በመቶ የስርጭት መጠን በ2024 ወደ 0 ነጥብ 85 በመቶ ቢቀንስም እንደየህብረተሰብ ክፍሎች አይነት፣ የሥራ ዘርፍ መጠኑ ሊጨምር እንደሚችል ነው የተጠቆመው።

እንደ የረጅም ርቀት አሽከርካሪዎች፣ የኢንዱስትሪ ሠራተኞች እና ወጣት ሴቶች ያሉ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ትኩረት የሚሹ እንደሆኑም ተነስቷል።

የኤድስ ሄልዝኬር ፋውንዴሽን የኤች አይ ቪ ስርጭትን ለመቀነስ የቅስቀሳ ሥራዎች፣ ኮንዶም በአግባቡ መጠቀም፣ መደበኛ ምርመራዎች እና ተጋላጭ የሆኑ ሴቶችን በኢኮኖሚ መደገፍ ወሳኝ መፍትሄዎች መሆናቸውን አሳስቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...