የአያቶላህ አሊ ኻሜኒ ሚስት መገደላቻውን የኢራን ቴሌቪዥን አረጋገጠ

Date:

አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ በፈጸሙት ጥቃት የተገደሉት የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ሚስት መገደላቸውን የአገሪቱ መንግሥት ቴሌቪዥን አረጋገጠ።

የጠቅላይ መሪው ሚስት ማንሱሬህ ኾጃስቴ ባግሄርዛዴህ የተገደሉት “ቤታቸው ውስጥ” መሆኑን ቴሌቪዥን ጣቢያው ገልጿል። ቀደም ሲል የኢራን መገናኛ ብዙኃን ግለሰቧ “ኮማ” ውስጥ እንደነበሩ ዘግበው ነበር።

ቅዳሜ ዕለት በተፈጸመው ጥቃት ከአያቶላህ ኻሜኒ በተጨማሪ ሴት ልጃቸው፣ የልጃቸው ባል እና የልጃቸው ልጅ መገደላቸው ተዘግቧል።

የጠቅላይ መሪው ሚስት ከአያቶላህ ኻሜኒ አራት ወንዶች እና ሁለት ሴት ልጆች ነበሯቸው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል ጦር እሑድ በሊባኖስ፣ ቤይሩት ውስጥ በፈጸመው ጥቃት የሔዝቦላህን የደኅንነት ኃላፊ መግደሉን አስታውቋል።

የእስራኤል ጦር ኃይል “እሑድ ምሽት ቤይሩት ውስጥ በተፈጸመ የተነጣጠረ ጥቃት፣ የሔዝቦላህ የደኅንነት ተቋም አዛዥ የሆነውን ሽብርተኛው ሑሴን ማክሌድን መደምሰሱን አረጋግጧል” ሲል ባወጣው መግለጫ ላይ አስፍሯል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...