የአዲስ አበባ የገቢዎች በስምንት ወር 145.9 ቢሊዮን ብር ሰበሰበ

Date:

በ2017 በጀት ዓመት በአጠቃላይ 230.4 ቢሊየን ብረ ለመሰብሰቅ አቅዶ ወደ ስራ የገባው ቢሮው ይህንን እቅዱ ለማሳካትም የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ቆይቷል። በተለይም ከገቢ አሰባሰብ ጋር በተያያዘ ያሉትን ችግሮች በመለየት ለመፍታት ጥረት ተደርጓል የተባለ ሲሆን በዋነኛትም ከአሰራር፣ ከአደረጃጀትና ቴክኖሎጂን አጠቃቀም ብሎም ከሌብነትና ብልሹ አሰራር ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮችን በመለየት ለመፍታት የተለያዩ ስትራቴጂዎች መተግበራቸውን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ  የኮሙኒኬሽን ክፍል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

ቢሮው ባለፉት ስምንት ወራት 116.5 ቢልዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ ወደ ስራ የገባ ሲሆን ኪዚህም 113.7 ቢልዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን የገለት አቶ ሰውነት ይህም የእቅዱን 97.59 በመቶ ያሳካ ነው ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪ እንደ መሬት ልማት አስተዳደርና የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ቁጥጥር የመሳሰሉ በማዕከል ገቢ የሚሰበስቡ ተቋማት ደግሞ በስምንት ወሩ 37.9 ቢልዮን ብር ለመሰብሰብ አቅደው ሲሰሩ የነበሩት ሲሆን ከዚህ ውስጥ 31 ቢልዮን ብር በመሰብሰብ የእቅዳቸውን 81.7 በመቶ አሳክተዋል።

ሌሎች በክፈኮፍለ ከተማ ደረጃ ገቢ የሚሰበሰቡት እንደ የማዘጋጃ ቤት ያሉት ደግሞ ባለፉት ስምንት ወራት በክፍለ ከተማ ደረጃ ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረው 1.4 ቢልዮን ብር ሲሆን 1.2 ቢልዮን ብር ተሰብስቧል ይህም የእቅዱን 90.8 በመቶ ያሳካ ነው። በአጠቃላይ የአዲስ አበባ ከተማ የገቢዎች ቢሮ በስምንት ወር ውስጥ የእቅዱን 93.6 በመቶ ያሳካ መሆኑን አክለዋል።

ከዚህ ባለፈ ቢሮው የገቢ መሰረትን ለማስፋት፣ የእዳ ክትትልን አቅምን ለማሳደግ የተለያዩ የአሰራር ስርዓቶችን ለይቶ ወደ ተግባር ገብቷል ያሉ ሲሆን ከብልሹ አሰራር ጋር በተያያዘ በተለይም ከኦዲት ጥራት ጋር ተያያዞ የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ የኦዲት ጥራት የሚያረጋግጥ የስራ ክፍልን በማደረጃት ወደ ስራ መገባቱን አቶ ሰውነት አየለ ጨምረው ለብስራት ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...