የአፍሪካ ሕብረት ባወጣው መግለጫ በትግራይ ያለውን ሁኔታ እየተከታተለ እንደሆነ በመግለጽ የክልሉ ሰላም እና መረጋጋት ወሳኝ እንደሆነ ገልጧል፡፡
ሁሉም አካላት ከግጭት በመቆጠብ ውይይት እንዲያደርጉ እና የፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት እንዲገዙ ሕብረቱ አሳስቧል።
ለፕሪቶሪያ ስምምነት መገዛት የተገኘውን ሰላም ለመጠበቅ እና ለዘላቂ የሰላም ግንባታ፣ እርቅ እና ልማትን የሚደግፍ ሁኔታ ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑንም ገልጿል።
ከዚህ ባለፈ ህበረቱ ለስምምነቱ ትገበራ የማይቋረጥ ድጋፉን እንደሚቀጥልም አስታውቋል፡፡
