የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም ጉባዔ በአዲስ አበባ ይካሄዳል

Date:

39 አባል ሀገራት እና ሌሎች ባለድርሻዎች የሚሳተፉበት የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም (ARC-COP 16) ጉባዔ ከፊታችን ረቡዕ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል፡፡

የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ጉባኤው በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ከመጋቢት 30 እስከ ሚያዚያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ገልጿል።

የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማሪያም ጉባኤውን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት÷ ኢትዮጵያ በሰብዓዊ ድጋፍ ራሷን ለመቻል የምታደርገው ጥረትና የመጣው ውጤት በመድረኩ በተሞክሮነት ይቀርባል።

የአፍሪካን ችግር በአፍሪካውያን ለመፍታት ከሚሰራባቸው መስኮች መካከል በሰብዓዊ ድጋፍ ራስን መቻል አንዱ መሆኑን ጠቅሰው÷ በመድረኩ መግባባት ለመፍጠር ምክክር ይደረጋልም ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያከናወች ስራ እና ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለማሟላት የተገበረቻቸው ተግባራት ለጉባዔው አስተናጋጅነት ተመራጭ እንዳደረጋት አንስተዋል፡፡

የጉባኤው ተሳታፊዎች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጨምሮ በአዲስ አበባ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎችን እንዲጎበኙ በማድረግ ኢትዮጵያን የማስተዋወቅ ስራ እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አርሰናል ከቦርንማውዝ በጉጉት የሚጠበቅ ጨዋታ

በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን...

በአሜሪካ እና ኢራን ድርድር ላይ የሚነሱ አራት ቁልፍ ጥያቄ

በፓኪስታን የሚደረገው የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር እየተጠበበፓኪስታን ነገር ግን...

መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል...

የተመድ ዋና ጸሐፊ ኢራን እና አሜሪካ “በቅን ልቦና” ወደ ድርድሩ እንዲገቡ ጠየቁ

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን...