ባለፉት ጥቂት ዓመታት በተከናወኑ ጥልቅ የሪፎርም ስራዎች፣ በአንድ ጥላ ስር የሚገኙ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ውጤታማነታቸው በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ብሩክ ታዬ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-
የገቢ ዕድገት፦ የተቋማቱ አጠቃላይ ዓመታዊ ገቢ ከ704 ቢሊዮን ብር ወደ 2.1 ትሪሊዮን ብር አድጓል።
የታክስ ድርሻ፦ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ለሀገሪቱ የታክስ ገቢ ያላቸው ድርሻ 40 በመቶ ደርሷል።
ውጤታማነት፦ ቀደም ሲል በኪሳራ ውስጥ የነበረው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማሻሻያ ስራ ከተሰራበት በኋላ የ2.1 ቢሊዮን ብር ትርፍ አግኝቷል።
ግዙፍ ፕሮጀክቶች፦ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የወርቅ ማጣሪያ እና የክትባት ማምረቻን ጨምሮ 16 ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
በአፍሪካ ግዙፉ የሉዓላዊ ሀብት ፈንድ የሆነው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ፤ እንደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኢትዮ ቴሌኮም እና ንግድ ባንክ ያሉ ተቋማትን በማስተዳደር የሀገራችንን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ ይገኛል፡፡
