የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በአርሲ ሺርካ ለደረሰው ጥቃት መግለጫ አወጣ

Date:

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በኦሮሚያ ክልል፣ አርሲ ዞን፣ ሺርካ ወረዳ በንፁሐን የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ የደረሰውን አሰቃቂ ጥቃት አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

የምክር ቤቱ መግለጫ ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፡ *’ምክር ቤቱ በንፁሐን ወገኖቻችን ላይ በደረሰው አሰቃቂ አደጋ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማው ገልጿል። * ድርጊቱ የትኛውንም ሃይማኖት የማይወክል፣ ይልቁኑም በሃይማኖቶች መካከል ለዘመናት የኖረውን የመከባበር እሴት በመናድ፣ በአማኞች መካከል ጥርጣሬና ግጭት ለመፍጠር የተቀነባበረ እኩይ ሴራ መሆኑን ምክር ቤቱ አምኗል።

መንግስት አጥፊዎቹን በአፋጣኝ ለይቶ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድ ምክር ቤቱ በጥብቅ ጠይቋል። ለሟች ቤተሰቦች ፈጣሪ (አላህ) መፅናናቱን እንዲሰጥ ምክር ቤቱ ምኞቱን ገልጿል። Via የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...