አሜሪካ ኢራን ላይ “መጠነ ሰፊ ወታደራዊ እርምጃ” መውሰድ እንደምትቀጥል ትራምፕ ተናገሩ

Date:

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “በኢራን ላይ የሚወሰደው መጠነ ሰፊ ወታደራዊ እርምጃ” እንደሚቀጥል አስታወቁ።

የኢራን መንግሥት የኒውክሌር የጦር መሣሪያ ግንባታ እንዲያቆም ከአሜሪካ የተሰጠውን ማስጠንቀቂያ ችላ እንዳለም ገልጸዋል። ከቴህራን የተደቀነውን አደጋ ለመቀልበስ እርምጃ መውሰድ እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።

ለአሜሪካ ወታደሮች ሜዳልያ ለመስጠት በተዘጋጀ ሥነ ሥርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት ትራምፕ “የኢራን የሚሳዔል መርሃ ግብር የኒውክሌር ግንባታን ለመሸፈን ያለመ ነበር” ሲሉም ተደምጠዋል።

ኒውክሌር የጦር መሣሪያ እና የረዥም ርቀት ሚሳዔል የታጠቀ የኢራን መንግሥት መካከለኛው ምሥራቅ እና የአሜሪካ ሕዝብ “ሊታገሱት የማይገባ ስጋት ነው” ብለዋል።

በኢራን ላይ እየወሰዱ ያሉት እርምጃ አላማው የአገሪቱን “የሚሳዔል ግንባታ አቅም እንዲሁም የባሕር ኃይል ማምከን” መሆኑን ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።

“በተገደሉት የአሜሪካ ወታደሮች ስም ዘመቻውን አጠናክረን እንቀጥላለን” ብለዋል።

በኢራን ላይ እየተካሄደ ያለው ዘመቻ አሜሪካ ከያዘችው የጊዜ ሰሌዳ “በጣም እንደቀደመ” ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።

ዘመቻው ከመነሻው ላይ ከአራት እስከ አምስት ሳምንት እንደሚወስድ እንደተገመተ የጠቀሱት ትራምፕ “ከዚያም በላይ የመዝለቅ አቅም አለው” ሲሉ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...