የእስራኤል አምባሳደር ከስብሰባ ተገደው ወጡ

Date:

በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር የሆኑት ቤተ እስራኤላዊው አብርሃም ንጉሴ ዛሬ አፍሪካ ኅብረት የሩዋንዳውን የዘር ጭፍጨፋ ለማሰብ ካዘጋጀው ስብሰባ ተገደው እንዲወጡ ተደርገዋል።

አምባሳደር ከስብሰባው እንዲወጡ የተገደዱት፣ እስራኤል በጋዛ ፍልስጤማዊያን ላይ የምትፈጽመውን መጠነ ሰፊ ጥቃት የሚቃወሙ በርካታ አባል አገራት አምባሳደሩ በተገኙበት ስብሰባ ላይ አንካፈልም ብለው ተቃውሞ በማሰማታቸውን እንደሆነ ተገልጧል።

የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ አምባሳደሩ ከስብሰባው ተገደው መውጣታቸውን ተከትሎ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሃሙድ የሱፍን መውቀሱን የእስራኤል ጋዜጦች ዘግበዋል።

ሚንስቴሩ፣ ድርጊቱ የዘር ጭፍጨፋ የደረሰባቸውን የሩዋንዳ ቱትሲዎች መታሰቢያ ክብር ያልሰጠ፣ ተቀባይነት የሌለውና፣ የሩዋንዳና አይሁድ ሕዝቦችን ታሪክ ግምት ውስጥ ያላስገባ ነው በማለት መተቸቱን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

እስራኤል በድርጊቱ አሳሳቢነት ዙሪያ በዲፕሎማሲያዊ መስመሮች እንደምትገልጽ ጠቁማለች ተብሏል። አብርሃም የእስራኤል አምባሳደር ሆነው የተሾሙት፣ ባለፈው ዓመት ነሃሴ ነበር። [ዋዜማ]

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...