የእስራኤል አምባሳደር ከስብሰባ ተገደው ወጡ

Date:

በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር የሆኑት ቤተ እስራኤላዊው አብርሃም ንጉሴ ዛሬ አፍሪካ ኅብረት የሩዋንዳውን የዘር ጭፍጨፋ ለማሰብ ካዘጋጀው ስብሰባ ተገደው እንዲወጡ ተደርገዋል።

አምባሳደር ከስብሰባው እንዲወጡ የተገደዱት፣ እስራኤል በጋዛ ፍልስጤማዊያን ላይ የምትፈጽመውን መጠነ ሰፊ ጥቃት የሚቃወሙ በርካታ አባል አገራት አምባሳደሩ በተገኙበት ስብሰባ ላይ አንካፈልም ብለው ተቃውሞ በማሰማታቸውን እንደሆነ ተገልጧል።

የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ አምባሳደሩ ከስብሰባው ተገደው መውጣታቸውን ተከትሎ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሃሙድ የሱፍን መውቀሱን የእስራኤል ጋዜጦች ዘግበዋል።

ሚንስቴሩ፣ ድርጊቱ የዘር ጭፍጨፋ የደረሰባቸውን የሩዋንዳ ቱትሲዎች መታሰቢያ ክብር ያልሰጠ፣ ተቀባይነት የሌለውና፣ የሩዋንዳና አይሁድ ሕዝቦችን ታሪክ ግምት ውስጥ ያላስገባ ነው በማለት መተቸቱን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

እስራኤል በድርጊቱ አሳሳቢነት ዙሪያ በዲፕሎማሲያዊ መስመሮች እንደምትገልጽ ጠቁማለች ተብሏል። አብርሃም የእስራኤል አምባሳደር ሆነው የተሾሙት፣ ባለፈው ዓመት ነሃሴ ነበር። [ዋዜማ]

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የክሪፕቶ ሥራ ፈጣሪው የ15 ዓመት እስር ተፈረደበት

የቀድሞው የክሪፕቶከረንሲ ሥራ ፈጣሪ ተሰውሯል ከተባለ 40 ቢሊየን ዶላር...

5ኛው የኢሰመኮ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል ተካሄደ

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አዘጋጅነት በየዓመቱ በፈረንጆቹ ታኅሣሥ...

የንግድ ሚኒስቴር 13 ምርቶችን በመነሻ ሀገር የጥራት ማረጋገጫ (PVoC) እንዲያገኙ ወሰነ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት፣ በሀገር...

ገዳ ባንክ ከ444 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለፀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፤ ባንኮች የተከፈለ ካፒታላቸውን በ2018 ዓ.ም...