በአዲስ አበባ 35 ሺሕ መምህራን በልዩ መታወቂያ የትራንስፖርት አገልግሎት እያገኙ መሆኑ ተገለጸ

Date:

በአዲስ አበባ ከተማ 35 ሺሕ መምህራን በልዩ መታወቂያ ከክፍያ ነፃ የሆነ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጣቸው መሆኑን የአንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አካሉ አሰፉ እንደገለጹት፤ በቀደመው በጀት ለአንድ መምህር በቀን 16 ብር ተመድቦ የትራንስፓርት አገልግሎት እንዲያገኙ እየተደረገ ይገኛል።

ይህ በጀት በአሁኑ ወቅት ወደ አንድ ቦታ ለመድረስ እንኳን የማይበቃ ሊሆን እንደሚችል የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ ወጪው ከተመደበው በጀት ጋር የማይጣጣም መሆኑን ጠቁመዋል።

መምህራን የሕዝብ አገልጋይና ዜጋን የመገንባትና የማነፅ ሚና ያላቸው በመሆኑ፤ ልዩ መታወቂያው ከክፍያ ነፃ የትራንስፓርት አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ገልጸዋል።

በዚህም “መምህራንን ተጠቃሚ ማድረግ ልጆቻቸውን ማስተማር የማይችሉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ ማድረግ መሆኑ ልብ ሊባል ይገባል” ሲሉ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልጸዋል።

የከተማ አስተዳደሩም ይሄን ታሳቢ በማድረግ ሥራዎችን እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...