የዓለም የቡና ዋጋ መቀነሱን ተከትሎ ለዘርፉ ተዋናዮች መመርያ ተላለፈ

Date:

ማኅበሩ ከሁለት ቀናት በፊት ባወጣው አስቸኳይ መልዕክት፣ በአሁኑ ወቅት የዓለም የቡና ገበያ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ እንደሚገኝ ጠቁሟል፡፡

ምርት ሳይሸጥ በእጅ ላይ መቆየቱ ለከፋ የገንዘብ ኪሳራ ከመዳረጉ ባለፈ በሕግም ተጠያቂ ሊያደርግ እንደሚችል ማስጠንቀቁ ተዘግቧል፡፡

የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለሥልጣን፣ ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ዕለት የዓለም አቀፍ የቡና ገበያ ለውጥን እና የኢትዮጵያን የቡና ዘርፍ ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤ የቡና አቅራቢዎች፣ ላኪዎች እና አርሶ አደሮች ያከማቹትን ቡና ሽያጩን በማፋጠን ወደ ማዕከላዊ ገበያ እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርቧል።

ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ የዓለም አቀፍ የቡና ዋጋ ከአራት ዶላር አካባቢ ወደ 2.80 ዶላር ዝቅ ያለ ሲሆን ዋጋው ይበልጥ ቀንሶ ወደ 2.50 ዶላር ሊወርድ እንደሚችል የሚጠቁሙ ግምቶች በዘርፉ ተዋንያን ላይ ተጨማሪ ጫና እየፈጠሩ መሆኑንም አክለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...