- በኢራን ደቡብ ፓርስ የጋዝ ማምረቻ ስፍራ የሚገኘው የፔትሮኬሚካል ተቋም የአየር ድብደባ እንደተፈጸመበት ከእስላማዊው አብዮታዊ ዘብ ጋር ግንኙነት ያለው ታስኒም የዜና ወኪል ዘገበ።
- ኳታር፤ እስራኤል በተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ ስፍራው ላይ የፈጸመችውን ጥቃት “አደገኛ እና ኃላፊነት የጎደለው” ስትል ኮንናለች።የታስኒም ዘገባ እንደሚያመለክተው ጥቃቱ የተፈጸመው ዛሬ ረፋድ አካባቢ ነው።
- ከፊል ይፋዊው ፋርስ የዜና ወኩል በበኩሉ በቴሌግራም ገጹ ባወጣው ማስጠንቀቂያ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻው በእሳት መያያዙን ገልጿል። የእሳት እና የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች በስፍራው እንደሚገኙም ጠቅሷል።
- በዓለም ትልቁ በሆነው የተፈጥሮ ጋዝ ማውጫ ስፍራ ደቡብ ፓርስ ውስጥ የኳታር እና ኢራን ማምረቻ ተቋማት ይንቀሳቀሳሉ።ኳታር በመግለጫዋ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻው ስፍራ ላይ ጥቃት የተፈጸመው በእስራኤል እንደሆነ የገለጸች ሲሆን፣ ድርጊቱንም “አደገኛ እና ኃላፊነት የጎደለው” ስትል አውግዛለች።
- የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ማጅድ አል አንሳሪ፤ በኢነርጂ መሠረተ ልማት ላይ የሚፈጸም ጥቃት “የዓለም የነዳጅ ደኅንነት ላይ ስጋት እንደሚደቅን” ተናግረዋል።
- “ከዚህ በፊትም በተደጋጋሚ እንደገለጽነው ወሳኝ ተቋማትን ዒላማ ከማድረግ መቆጠብ እንደሚስፈልግ እንገልጻለን” ያሉት ቃል አቀባዩ፤ “ሁሉም ወገኖች” ዓለም አቀፍ ሕግን እንዲያከብሩ እና ውጥረቱን ለማርገብ እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
- BBC
በኢራን የሚገኘው የዓለም ግዙፉ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ ስፍራ ጥቃት ተፈጸመበት
Date:
