የአሜሪካ እና የደቡብ አፍሪካ ዲፕሎማሲያዊ ሁኔታ ተጋግሎ በአሜሪካ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሊባረሩ መሆኑን የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታውቀዋል።
ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ የደቡብ አፍሪካውን አምባሳደር ኢብራሒም ራሱልን “በታላቋ አገራችን ተቀባይነት የላቸውም” ሲሉ ተደምጠዋል።
ማርኮ ሩቢዮ፣ አምባሳደሩ አሜሪካን እንዲሁም ዶናልድ ትራምፕን የሚጠሉ ናቸው ሲሉ ገልፀው “ዘረኛ ፖለቲከኛ” ሲሉም በኤክስ ገፃቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ወርፈዋቸዋል።
በጋዛ በሚደረገው ጭፍጨፋ ቅይይማቸው የጀመረው አገራቱ ትራምፕ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ደግሞ የተለያዩ ምክኒያቶች ታክለውባቸው ግንኙነታቸውን ውጥረት የተሞላበት አድርጎታል።
