የጃፓን መንግስት ለኢትዮጵያ አርሶ አደሮች ተደራሽ የሚሆን ከ63ሺህ ኩንታል በላይ የዩሪያ አፈር ማዳበሪያ ድጋፍ አድርጓል።
የማዳበሪያ ርክክቡ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ፣ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺቢታ ሂሮናሪ በተገኙበት ተከናውኗል።
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታዋ ሶፊያ ካሳ የጃፓን መንግስት ላደረገው ድጋፍ አመስግነው፤ የአፈር ማዳበሪያው ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ሚኒስቴሩ ይሰራል ብለዋል።
በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺቢታ ሂሮናሪ በበኩላቸው፤ መንግስታቸው ግብርናን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ስለመናገራቸው የኢ.ቢ.ሲ መረጃ ያመለክታል፡፡
