የጃፓን መንግስት ለኢትዮጵያ ከ63ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ድጋፍ አደረገ

Date:

የጃፓን መንግስት ለኢትዮጵያ አርሶ አደሮች ተደራሽ የሚሆን ከ63ሺህ ኩንታል በላይ የዩሪያ አፈር ማዳበሪያ ድጋፍ አድርጓል።

የማዳበሪያ ርክክቡ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ፣ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺቢታ ሂሮናሪ በተገኙበት ተከናውኗል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታዋ ሶፊያ ካሳ የጃፓን መንግስት ላደረገው ድጋፍ አመስግነው፤ የአፈር ማዳበሪያው ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ሚኒስቴሩ ይሰራል ብለዋል።

በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺቢታ ሂሮናሪ በበኩላቸው፤ መንግስታቸው ግብርናን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ስለመናገራቸው የኢ.ቢ.ሲ መረጃ ያመለክታል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...