የግብዓት ዋጋ እስከ 400 በመቶ በመጨመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች እንዲጓተቱ ምክንያት ሆኗል

Date:

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እንደገለፀው የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ እስከ 400 በመቶ መጨመሩ የመንገድ ግንባታው የሚፈለገውን ደረጃ ላይ እንዳይደርስ ምክንያት ሆኗል።

ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ እንደተናገሩት ይህንን ችግር ለመቅረፍ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በማቆም ነባሮችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም ቃል የተገቡ ሁሉም የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይጠናቀቁ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።

የምክር ቤት አባላትም ከ1980 ጀምሮ በጥናት የተለዩ መንገዶች እንዳልተገነቡ፣ የተጀመሩት በጊዜያቸው አለመጠናቀቃቸውንና የተሰሩትም ሳይገለገሉ መበላሸታቸውን አንስተዋል። በተጨማሪም ለመንገድ ልማት የተነሱ ዜጎች ለዓመታት ካሳ ሳይከፈላቸው መቆየታቸውንም ካፒታል ሰምቷል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን በበኩላቸው የመንገድ ግንባታ መጓተት የካሳ ክፍያና የግንባታ ግብዓት አቅርቦት ችግር መሆኑን አምነዋል። ችግሩን ለመፍታትም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...