የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት እየተከበረ ነው፡፡
በዓሉ በተለይም በአዲስ አበባ ጃንሜዳ እና በጎንደር የእምነቱ ተከታዮችና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች በተገኙበት በድምቀት በመከበር ላይ ይገኛል፡፡
እንዲሁም በዝዋይ ሐይቅ ደሴቶችና በምንጃር ሸንኮራ ኢራምቡቲ በድምቀት እየተከበረ ሲሆን፥ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ነው በሀይማኖታዊ ስነስርዓት እየተከበረ የሚገኘው፡፡
ትናንት የጥምቀት ከተራ በዓል በመላ ሀገሪቱ የተከበረ ሲሆን፥ በዚህም ታቦታቱ ከየአብያተክርስቲያናቱ ወጥተው ወደየማደሪያቸው ባህረ ጥምቀት ገብተዋል።
በዛሬው ዕለትም በባህረ ጥምቀት ስፍራ በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
