የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

Date:

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት እየተከበረ ነው፡፡

በዓሉ በተለይም በአዲስ አበባ ጃንሜዳ እና በጎንደር የእምነቱ ተከታዮችና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች በተገኙበት በድምቀት በመከበር ላይ ይገኛል፡፡

እንዲሁም በዝዋይ ሐይቅ ደሴቶችና በምንጃር ሸንኮራ ኢራምቡቲ በድምቀት እየተከበረ ሲሆን፥ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ነው በሀይማኖታዊ ስነስርዓት እየተከበረ የሚገኘው፡፡

ትናንት የጥምቀት ከተራ በዓል በመላ ሀገሪቱ የተከበረ ሲሆን፥ በዚህም ታቦታቱ ከየአብያተክርስቲያናቱ ወጥተው ወደየማደሪያቸው ባህረ ጥምቀት ገብተዋል።

በዛሬው ዕለትም በባህረ ጥምቀት ስፍራ በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...