የጥርስ ህክምና ማስታወቂያዎች አብዛኛዎቹ ግነት ይታይባቸዋል

Date:

በዛሬዉ ዕለት የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የጥርስ ህክምና ማህበር ጋር በመሆን የጥርስ ህክምና አገልግሎት መስጫ ጤና ተቋማት ባለቤቶችና በጤና ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በጤና ተቋማት የሚሰሩ ማስታወቂያዎች በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ግምገማ አካሄዷል ።

በዉይይቱም በማህበራዊ ሚዲያ የሚተላለፋ የጥርስ ህክምና ማስታወቂያዎችን ጨምሮ አብዛኛዎቹ ማስታወቂያዎች ግነት የበዛባቸው መሆኑንና አንዳንዶቹም ከባህላችን የወጡ መልዕክቶችን ያዘሉ መሆናቸዉን በጤና ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ዮርዳኖስ አለባቸዉ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።

የጥርስ ህክምና ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ዶክተር ሜሮን ያዕቆብ በበኩላቸው ከጥርስ ህክምና ጋር  የተያያዙ ወጣ ያሉ የማስታወቂያ ስራዎችን በተመለከተ የሚስተዋሉ ግነቶች መዘዝ ሳያመጡና ወደ ሌሎችም ሙያዎች ሳያዛመቱ እንዴት ወደ መስመር ማስገባትና መቆጣጠር ይቻላል የሚለዉ ላይ ለመወያየት የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን ገልፀዋል ።

በተለያዩ ማሕበራዊ ሚዲያዎች የሚተላለፉ ማስታወቂያዎች ግነት የበዛባቸዉ ከመሆናቸዉ ባሻገር ከማህበረሰባችን ባህልና ወግ የወጡ አንዳንዶቹም ሀሰተኛ መረጃዎችን የሚይዙ በመሆናቸዉ ትኩረት በመስጠት የማስታወቂያ ኢንዱስትሪው ላይ እንዴት እንስራ የሚለዉ ላይ ሰፊ ዉይይት ተካሄዷል።
#ዳጉ_ጆርናል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...