የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል መንግስት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ስርዓት ለመደንገግ የወጣውን ማሻሻያ አዋጅ ተወያይቶ አጽድቋል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 22ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡
ምክር ቤቱ በዚሁ መደበኛ ስብሰባው የፌደራል መንግስት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ስርዓት ለመደንገግ የወጣ ማሻሻያ አዋጅ ላይ ተወያይቷል።
የማሻሻያ አዋጁ ከዚህ ቀደም በነበረው አዋጅ ላይ በትግበራ ላይ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በዚህም በምክር ቤቱ ውይይት ከተደረገበት በኋላ በሁለት ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ አዋጁ አጽድቋል፡፡
