የፌደራል መንግስት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ስርዓት ለመደንገግ የወጣ ማሻሻያ አዋጅ ፀደቀ

Date:

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል መንግስት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ስርዓት ለመደንገግ የወጣውን ማሻሻያ አዋጅ ተወያይቶ አጽድቋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 22ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡

ምክር ቤቱ በዚሁ መደበኛ ስብሰባው የፌደራል መንግስት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ስርዓት ለመደንገግ የወጣ ማሻሻያ አዋጅ ላይ ተወያይቷል።

የማሻሻያ አዋጁ ከዚህ ቀደም በነበረው አዋጅ ላይ በትግበራ ላይ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በዚህም በምክር ቤቱ ውይይት ከተደረገበት በኋላ በሁለት ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ አዋጁ አጽድቋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...