የፍልስጤማውያን ወደ ጋዛ መመለስ

Date:

በጋዛ የተኩስ አቁም ተግባራዊ መሆን በመጀመሩ በሺዎች የሚቆጠሩ የተፈናቀሉ ፍልስጤማውያን ወደ ሰሜናዊ ጋዛ መመለስ ጀመሩ፡፡

በእስራኤልና ሀማስ መካከል ያለውን ግጭት እንዲቋጭ በአሜሪካ የቀረበው የሰላም ስምምነት የመጀመሪያው ምዕራፍ መተግበር በመጀመሩ ነው ፍልስጤየማውያን ወደ ሰሜን ጋዛ መመለስ የጀመሩት፡፡

የእስራኤል መንግሥት ተኩስ ማቆም እና ታጋቾችን ብሎም እስረኞችን ለመፍታት የሚያስችለውን የጋዛ ስምምነት የመጀመሪያ ምዕራፍ በትናንትናው እለት ማፅቀዱ ይታወሳል፡፡

በዚህም የእስራኤል ጦር ወደ ተስማሙበት መስመር ወደ ኃላ አፈግፍገዋል። የተኩስ አቁሙ ስምምነት መጀመር ከፍተኛ መጠን ያለው የሰብዓዊ እርዳታ ወደ ጋዛ እንዲገባ በር ይከፍታል ነው የተባለው።

በዕቅዱ ውሎች መሠረት ሐማስ በሕይወት የሚገኙትን 20 የእስራኤል ታጋቾች በ72 ሰዓታት ውስጥ ይለቃል ተብሎ ይጠበቃል።

የእስራኤል መንግስት በበኩሉም በእስር ላይ የሚገኙ 250 ፍልስጤማውያንን እንዲሁም በጦርነቱ ወቅት በጋዛ ታስረው የሚገኙ ተጨማሪ 1,700 እስረኞችን ይለቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ዘገባው የቢቢሲ ነው NBC Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...