ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

Date:

በሀገራችን የባህል ሙዚቃ ዘርፍ ታዋቂነትን ያተረፈውና በብዙሃን ዘንድ ሰሜ ባላገሩ”እየተባለ በሚጠራው ተወዳጁ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እንገልጻለን።

ባደረበት የድንገተኛ ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ የቆየው ድምጻዊው፣ በተወለደ በዛሬው ዕለት (ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም) በተደረገለት የህክምና ክትትል ህይወቱ ማለፉን የቅርብ ቤተሰቦቹ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያን ባህል፣ ወግና ታሪክ የሚያንጸባርቁ በርካታ የሙዚቃ ስራዎችን ለአድማጮች ያበረከተው ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው፣ በሙዚቃው ኢንደስትሪ ውስጥ የራሱን ደማቅ አሻራ ጥሎ ማለፍ የቻለ ከያኒ ነበር።

ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት እንደነበር ከቤተሰቦቹ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለመላው የኪነ-ጥበብ አድናቂዎቹ በሙሉ መጽናናትንና ብርታትን ይመኛል። ፈጣሪ ነፍሱን በገነት ያኑራት።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...

“ንባብ ለህይወት!” ታላቅ የንባብ ሳምንት እና የመጻሕፍት አውደ ርዕይ

የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት እና የንባብ ለህይወት...

በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2...