በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ከዛሬ ሰኔ 8 እስከ ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በተለያዩ የፈተና ጣቢያዎች መሰጠት ጀምሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክብር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በዳግማዊ ሚኒሊክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመገኘት ፈተናውን በይፋ አስጀምረዋል።
👉🏼 85,017 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች በከተማ ደረጃ ፈተናውን ይወስዳሉ።
👉🏼 በአጠቃላይ በ199 የፈተና ጣቢያዎች ፈተናው እየተሰጠ ይገኛል።
ፈተናው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በየደረጃው የኮማንድ ፖስት አደረጃጀት ተዋቅሮ የጸጥታ አካላትና ልምድ ያላቸው አስፈጻሚዎች ተመድበዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የተማሪዎች የምገባ አገልግሎት፣ የዩኒፎርምና የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉ ለውጤት መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጉ ተገልጿል። ዘንድሮም ከተደረገው ዝግጅት አንጻር የተሻለ ውጤት እንደሚጠበቅ ተጠቁሟል።
