በጥበብ አፍቃሪያኑና በጥበበኛው ዘንድ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠበቀው ’The Big Art Sale’ ዓውደ ርዕይ በዚህ ዓመት ለሃያኛ ጊዜ በሒልተን ሆቴል የፊታችን ሚያዝያ 4 እና 5 2017 ዓ.ም ይካሄዳል።
በአውደ ርዕዩ ከ100 በላይ ሰዓሊያንና ቀራፂያን አዳዲስ ሥራዎቻቸውን ለጎብኚዎችና ለገዢዎች ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
ከጥበብ ስራዎች በተጨማሪ ጥበብ አፍቃሪያኑ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የሚዝናኑባቸው የመጠጥና የምግብ ኮርነሮች ሲኖሩ፤ለልጆች ልዩ የመጫወቻ ሥፍራም ተዘጋጅቶ ይጠብቃቸዋል ተብሏል፡፡
ይህ ልዩ ዓውደ ርዕይ ጠቢብያኑ ሥራቸውን እንዲሸጡ እድል የሚሰጣቸው ሲሆን፤ ገቢውም ለበጎ አድራጎት ሥራዎች እንደሚውል ተጠቁሟል።
በዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄደው የጥበብ ዓውደርዕዩ ዋትስ አውት አዲስ ከሒልተን ሆቴል ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ነው።
