” ግጭቱ ቆሟል ሕዝብ የማወያየትና የሞቱትን የመቅበር ስራ ሲሰራ ነዉ የዋለው ” – የደራሼ ወረዳ ነዋሪዎች

Date:

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ በጋርዱላ ዞን ደራሼ ወረዳ ከመጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በተቀሰቀሰ ግጭት የሰዎች ሕይወት መጥፋቱና በርካታ ቤቶች መቃጠላቸዉን የአከባቢውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መናግራቸው ይታወሳል።

በወረዳዉ የሀይ’በረና እና ኦኖታ አከባቢ ነዋሪዎች ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት ግጭቱ የመከላከያ ሰራዊት ወደ አከባቢው በመግባቱ መቆሙን ተናግረዋል።

በግጭቱ ምክንያት ሕይወታቸዉን ያጡትን የመቅበርና ሕዝቡን የማረጋጋት ስራ እየተሰራ መዋሉንም ገልጸዋል።

” የሞተዉ ሰዉ ቁጥር በጣም ብዙ ነዉ አስከሬናቸው እየተፈለገ ያሉም አሉ ” ያለን አንድ የአከባቢው ነዋሪ ” የተቃጠለዉ ቤት ብዛት ከቁጥር በላይ ነዉ ” ሲሉ ሁኔታዉን አብራርተዋል።

” የኛ ሁለት አጎቶች እስካሁን የገቡበት አልታወቀም፣ ልክ ግጭቱ እንደቆመ ቤተሰብ እያፈላለግን ነዉ ” ያለን ሌላኛዉ አስተያየት ሰጪ ” አሁን እየመሸ ስለሆነ የምናገኝ አይመስለንም፣ ሞተዉ ይሁን በህይወት ያሉ ፈጣሪ ነዉ የሚያዉቀዉ ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዋሪዎችን ሃሳብ ተከትሎ በድጋሚ ወደ ጋርዱላ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ብርሃኑ ኩናሎ ደዉሎ የነበረ ሲሆን ሕዝብ እያወያዩ ብቻ እንደሆነ በመግለፅ ከዚህ ያለፈ መረጃ ለመስጠት እንደማይችሉ ገልፀዋል።

ከቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ ከኢራን ጋር የተስማሙባቸውን ነጥቦች ከአርብ በፊት ይፋ ሊያደርጉ ይችላሉ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነቱን ለማቆም የተስማሙባቸውን...

‹‹ሃገረ ትግራይ›› በዘመናት መነፅር ሲታይ

(አጭርዳሰሳ) በወሰንሰገድ ገ/ኪዳን (ጋዜጠኛ) የመጽሐፉርዕስ፡- ሃገረ ትግራይ የመጽሐፉ ዓይነት፡-...

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...