ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ሰአር ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በኢትዮጵያ ጉብኝት በማድረግ ላይ ካሉት የእሥራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በኢትዮ-እሥራኤል ግንኙነት ላይ ፍሬያማ ውይይት ማካሄዳቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ሁለቱ ሀገሮቻችን በታሪክ ሥረ መሠረት ላይ የተገነባ ረዥም ዘመን የቆየ ግንኙነታቸውን ዛሬም ቀጥለዋል ብለዋል።
ዛሬ ትብብራችን በኢኮኖሚያዊ፣ በፖለቲካዊ፣ በዲፕሎማሲያዊ፣ በማኅበራዊ እና በሌሎችም መስኮች ላይ ተጠናክሮ ቀጥሏል ሲሉም ገልጸዋል።
