ፈረንሳይ ለፍልስጤም እውቅና እንደምትሰጥ ገለፀች

Date:



ፈረንሳይ በመስከረም ወር ለፍልስጤም መንግስት በይፋ እውቅና እንደምትሰጥ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ይህን የሚያደርጉ ከሆነም ፈረንሳይ ይህን በማድረግ የመጀመሪያዋ የG7 ሀገር ትሆናለች ።

ማክሮን በኤክስ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍ በትክክለኛ መንገድ  በኒውዮርክ በተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንደሚያሳውቁ ተናግረዋል።

አሁን ላይ የሚያስፈልገው የጋዛ ጦርነት እንዲያበቃ ማድረግ እና ነዋሪዎችን መታደግ ነውም ብለዋል።

እንዲሁም አስቸኳይ የተኩስ አቁም፣ ሁሉንም ታጋቾች መልቀቅ እና ለጋዛ ህዝብ ትልቅ ሰብአዊ እርዳታ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ  ባሰፈሩት ፅሁፍ ጠቅሰዋል።

የፍልስጤም ባለስልጣናት የማክሮንን ውሳኔ የተቀበሉ ሲሆን የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ  ግን እርምጃው “ሽብርን ያበረታታል” ሲሉ መግለፃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ሐምሌ 18/2017 ዓ.ም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...