ፈረንሳይ ለፍልስጤም እውቅና እንደምትሰጥ ገለፀች

Date:



ፈረንሳይ በመስከረም ወር ለፍልስጤም መንግስት በይፋ እውቅና እንደምትሰጥ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ይህን የሚያደርጉ ከሆነም ፈረንሳይ ይህን በማድረግ የመጀመሪያዋ የG7 ሀገር ትሆናለች ።

ማክሮን በኤክስ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍ በትክክለኛ መንገድ  በኒውዮርክ በተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንደሚያሳውቁ ተናግረዋል።

አሁን ላይ የሚያስፈልገው የጋዛ ጦርነት እንዲያበቃ ማድረግ እና ነዋሪዎችን መታደግ ነውም ብለዋል።

እንዲሁም አስቸኳይ የተኩስ አቁም፣ ሁሉንም ታጋቾች መልቀቅ እና ለጋዛ ህዝብ ትልቅ ሰብአዊ እርዳታ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ  ባሰፈሩት ፅሁፍ ጠቅሰዋል።

የፍልስጤም ባለስልጣናት የማክሮንን ውሳኔ የተቀበሉ ሲሆን የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ  ግን እርምጃው “ሽብርን ያበረታታል” ሲሉ መግለፃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ሐምሌ 18/2017 ዓ.ም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...