ፕሪሚየር ስዊች ሶሉሽንስ እና ማስተር ካርድ ደህንነቱ የተጠበቀ የኦንላይን አገልግሎት አስጀመሩ

Date:

ፕሪሚየር ስዊች ሶሉሽንስ (PSS) እና ማስተርካርድ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የዲጂታል ክፍያ ማረጋገጫ ስርዓት ይፋ አደረጉ።

በEMV 3-D Secure (3DS) ቴክኖሎጂ ላይ የተመሠረተው ይህ አዲስ አገልግሎት፣ እየጨመረ የመጣውን የኦንላይን ክፍያ ማጭበርበር ስጋት ለመቀነስ እና የኢ-ኮሜርስ ንግድን ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

የPSS ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አምሃ ታደሰ፣ ይህ ስርዓት ለሀገሪቱ የዲጂታል ኢኮኖሚ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። የማስተርካርድ ከፍተኛ ምክትል ፕሬዝዳንት ሸህሪያር አሊ በበኩላቸው፣ አገልግሎቱ የዲጂታል ሽግግርን ከማፋጠኑም በላይ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ሥነ-ምህዳር ለመፍጠር እንደሚረዳ ተናግረዋል።

አዲሱ ስርዓት ለነጋዴዎች፣ ለባንኮች፣ ለፊንቴክ ኩባንያዎች እና ለደንበኞች ከፍተኛ ጥቅም እንደሚሰጥም ተጠቅሷል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...