ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከተባበሩት ዓረብ ኤሜሬቶች ጋር የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስምምነት መፈራረማቸውን አስታወቁ

Date:

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶችን በጎበኙበት ወቅት የ200 ቢሊዮን ዶላር የንግድ ስምምነቶች ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።

ከእነዚህ ስምምነቶች መካከል ሁለቱ ሀገራት በሰው ሰራሽ አስተውሎት አብሮ መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት መፈጸማቸው ተነግሯል።

የአሜሪካ የንግድ ዲፓርትመንት እንደገለፀው፤ አሜሪካ እና የተባበሩት ዓረብ ኢምሬትስ “ዩኤስ-ዩኤኢ አክስለሬሽን ፓርትነርሺፕ” የተባለ ልዩ አጋርነት ለመፍጠር ተስማምተዋል። ይህ አጋርነት ሀገራቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ ተቀራርበው እንዲሰሩ ያግዛል ተብሏል።

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ፕሬዚዳንት ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ በአቡ ዳቢ የሚገኘው አዲሱ ባለ 5-ጊጋዋት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዕከል ምዕራፍ አንድ መክፈቻ ላይ ተገኝተዋል።

ይህ አዲስ ባለ 5-ጊጋዋት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዕከል ሲጠናቀቅ ከአሜሪካ ውጭ የሚገኝ በዓለም ላይ ትልቁ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መገልገያ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...