ፖሊስ የአዲስ ስታንዳርድ ጋዜጠኞችን ለእስር መዳረጉን እና የኤሌክትሮኒክስ ንብረቶችን መውሰዱን በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ

Date:



በእስር ላይ የነበሩ የተቋማችን ሰራተኞች ምሽት ላይ ከተለቀቁ በኋላ ንብረቶቻችሁ ከማክሰኞ ሚያዚያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም በኋላ ሊመለሱላችሁ ይችሉ ይሆናል ተብለናል።

ተቋማችን አዲስ ስታንዳርድ ሚዲያ በግልጽ ለህዝብ ማሳወቅ የሚፈልገው የተቋማችን ዋነኛ የዲጂታል መገልገያችን (main digital credentials) ምንም አይነት ጥቃት እንዳይደርስበት በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲገኝ ያደረግን መሆኑን ነው።

ነገር ግን ከዚህ ውጭ ፖሊስ ባካሄደው ብርበራ በግዳጅ ከተወሰዱብን የኤሌክተሮኒክስ እቃዎች በተለይም ከስልኮቹ እና ኮምፒዩተሮቹ በተናጠል የሚላኩ ማናቸውም መልዕክቶች፣ ኢሜይሎች እንዲሁም ግንኙነቶች ተቋማችንን እንዲሁም ሰራተኞቻችንን የማይወክሉ መሆናቸውን ነው።

በተቋማችን ላይ ፖሊስ ብርበራ ካካሄደ በኋላ ባሉት ጊዜያት እነዚህ ኮምፒዩተሮች እና ስልኮች የሚገኙት በጸጥታ ሀይሎቹ እጅ ሲሆን በእነዚህ ኮምፒዩተሮች እና ስልኮች ምን እየተከናወነባቸው እንደሆነ የተረጋገጠ ነገር መግለጽ አንችልም።

ሆን ተብሎ በፋሲካ ዋዜማ እንዲህ አይነት ድርጊት በተቋማችን ላይ የተፈጸመው አፋጣኝ ምላሽ እንዳንሰጥ እና ሰራተኞቻችን ግራ እንዲጋቡ ለማድረግ መሆኑን መረዳት አያዳገትም።

በዚህ አጋጣሚ ህጋዊ እና ሰላማዊ የሆነ አካሄድን አሟጦ በመጠቀም የሰራተኞቻችን ደህንነት እና የኤሌክተሮኒክስ ንብረቶቻችንን ያለምንም ጥቃት መመለስ ለማረጋገጥ እንደምንሰራ ለማሳወቅ እንወዳለን።

በዚህ ፈታኝ ጊዜ የሚዲያ ተቋማችን ወዳጆች ሁኔታዎቹን እንድትረዱልን እያሳሰብን፣ ቀጣይነት ላለው ድጋፋችሁ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

በየጊዜው የሚኖሩ ሁኔታዎችን እየተከታተልን እንደምናሳውቅ እንገልጻለን።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የክሪፕቶ ሥራ ፈጣሪው የ15 ዓመት እስር ተፈረደበት

የቀድሞው የክሪፕቶከረንሲ ሥራ ፈጣሪ ተሰውሯል ከተባለ 40 ቢሊየን ዶላር...

5ኛው የኢሰመኮ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል ተካሄደ

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አዘጋጅነት በየዓመቱ በፈረንጆቹ ታኅሣሥ...

የንግድ ሚኒስቴር 13 ምርቶችን በመነሻ ሀገር የጥራት ማረጋገጫ (PVoC) እንዲያገኙ ወሰነ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት፣ በሀገር...

ገዳ ባንክ ከ444 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለፀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፤ ባንኮች የተከፈለ ካፒታላቸውን በ2018 ዓ.ም...