ቅዳሜ ከሰዓትዎን የዓድዋ ድል በዓል ምክንያት በማድረግ ባዘጋጀነው ልዩ ፕሮግራም ያሳልፉ ስለ ሀገራችን ማወቅ ያሉብንን እውነታዎች ምንድናቸው? እነሱንስ የምንገልጽባቸውን ወሳኝ ቃላት ምን ያህል እንግባባ’ባቸዋለን? ስሞችን በትክክል ካላወቅን ወይም የጋራ ስም ካልፈጠርን ለጋራ ሀገር በጋራ መሰለፋችንን እርግጠኛ መሆን ይቻላል ወይ?
ሀገር፣ ድንበር ፣ መንግሥት፣ ሕዝብ፣ ሉዓላዊነት ፣ ዜጋ፣ ጦርነት ፣ ወዘተ የሚሉ ስሞች ላይ የፖለቲካ፣ የታሪክ እና የሕግ ትንታኔ እንዲያቀርቡ ምሁራንን ጋብዘናል። ኑና ሀሳብ ተካፈሉ፣ አካፍሉ።
ለጋራ ሀገር ፡ የጋራ ቃላት ያስፈልጉናልና::
ርዕስ – “ሀገር እና ዓድዋ”
አወያይ:-
ፍሬው ማዕሩፍ
(ከ ሕግ ፍልስፍና)
አቅራቢዎች:-
ፕሮፌሰር አህመድ ዘከሪያ
/ከታሪክ አንፃር/
ፕሮፌሰር ብሩክ ኃይሉ
/ከፖለቲካ አንፃር/
የሕግ ባለሙያ አንዱዓለም በዕውቀቱ
(ከሕግ አንፃር
የካቲት 21 – ቅዳሜ ከቀኑ 8:30 ጀምሮ
ቦታ አራት ኪሎ ዋልያ አዳራሽ – ኢክላስ ሕንጻ 4ኛ ፎቅ
