ታዋቂው ሳይንቲስት አመሃ በላይ (ዶ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

Date:

በማይክሮ አልጌ ባዮቴክኖሎጂ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም ምሁር የነበሩት አመሃ በላይ (ዶ/ር) በተወለዱ በ79 ዓመታቸው፣ የካቲት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ዶ/ር አመሃ የቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ሲሆኑ፣ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ደግሞ ከዩናይትድ ኪንግደም አግኝተዋል።

ወደ ሀገራቸው በመመለስም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ13 ዓመታት በመምህርነትና በባዮሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊነት አገልግለዋል።

በሙያ ሕይወታቸው ከፍተኛ ዝና ያተረፉት፣ በካሊፎርኒያው “Earthrise Nutritionals” ተቋም ውስጥ ለ26 ዓመታት በከፍተኛ የቴክኖሎጂ መኮንንነት (CTO) በሰሩበት ወቅት ነው።

በዘርፉ ባላቸው ጥልቅ ዕውቀትና ለስፒሩሊና ኢንዱስትሪ ባበረከቱት አስተዋጽኦም “ሚስተር ስፒሩሊና” (Mr. Spirulina) የሚል ስያሜ እስከማግኘት ደርሰዋል።

ዶ/ር አመሃ በላይ ከዓለም አቀፍ ሥራቸው ባሻገር፣ ለሀገራቸው ኢትዮጵያ ባላቸው ጥልቅ ፍቅር ይታወቃሉ። የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ እና ዘላቂ ልማት ምክር ቤት መሥራች በመሆንም አገልግለዋል።

በተለይም በጣና ሐይቅ፣ በአባያ ሐይቅና በአዋሽ ወንዝ ላይ የተከሰተውን አደገኛ የእንቦጭ አረም ለመከላከል በሚደረገው ሳይንሳዊ ጥረት ውስጥ በንቃት ተሳትፈዋል።

የዶ/ር አመሃ በላይ የቀብር ሥርዓት ቅዳሜ፣ የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚፈጸም ታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...