አሜሪካ እንደገለጸችው ለእስራኤል ያቀረበችው አዲስ የጊዜያዊ የተኩስ አቁም እቅድ በእስራኤል በኩል ተቀባይነት አግኝቷል፡፡
የዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልእክተኛ ሲቭ ዊትኮፍ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ እንደገለጹት በሃማስና እስራኤል መጠነኛ ስምምነቶች ተፈጥረው የታገቱ ሰዎች ወደቤታቸው ሊመለሱ እንደሚችሉ ያላቸውን ተስፋ ገልጸው ነበር፡፡
አሁን ደግሞ የዋይታውስ ፕረስ ሴክሬታሪ ካሮሊን ሊቬት ለጋዜጠኞች እንዳሉት እስራኤል አዲሱን የጊዜያዊ የተኩስ አቁም እቅድ ተቀብላዋለች፡፡
ሃማስ በበኩሉ ምላሽ ለመስጠት አዲሱን ፕሮፖዛል በደምብ ለማጥናት ጊዜ እንደሚያስፈልገው ስለማስታወቁ የዘገበው አሶሼድ ፕረስ ነው፡፡
