ሃገራቱ እንደገለጹት ሩሲያና ሰሜን ኮሪያ ወታደራዊ ትብብራቸውን በማጠናከር ሰሜን ኮሪያ ዩክሬን ላይ የሚተኮሱ ሚሳኤሎችን ለሩሲያ እያቀረበች ነው ብለዋል፡፡
የመንግስታቱ ድርጅት ባለሞያዎች ባቀረቡት ሪፖርት ሰሜን ኮሪያ ከ2010 ጀምሮ የተጣሉባትን ማእቀቦች መጣስ እንደጀመረች ተገልጹል፡፡
በቀረበው የ29 ገጽ ሪፖርት ላይ እንደሰፈረው ሰሜን ኮሪያና ሩሲያ የተባበሩት መንግስታት ማእቀብ አድርጎ የጣለባቸውን ወታደራዊ ትብብር በመጣስ ግንኙነታቸውን ከየትኛውም ጊዜ በላይ ማጠናከራቸው ተነግሩዋል፡፡
የማእቀብ ገምጋሚዎቹ እንዳት ሰሜን ኮሪያ የጦር መሳሪያና ከጦርመሳሪያጋ የተገናኙ እቃዎችን ሚሳኤሎችን እዲሁም የጦር ተሸከርካራችን በባህር ባየርና በባቡር ለሩሲያ እያቀረበች ትገኛለች ብለዋል ዘገባው የ ያሁ ኒውስ ነው፡፡
