ባለፈው ሐሙስ ከአሰሪው ድርጅት ጋር ባለመግባባታቸው ስራ ያቆሙት የዲኤችኤል/DHL ሰራተኞች ከዛ በኋላ በተደረገ ድርድር የሰራተኛ ማህበሩና ድርጅቱ ስምምነት በ35% ጭማሪ መስማማታቸውን ቲክቫህ አስነብቧል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ የስራና ክህሎት ፅ/ቤት አሸማጋይነት የሰራተኛ ማህበሩ እና ድርጅቱ በ35% ጭማሪ ተስማምተዋል።የድርጅቱ ሰራተኞች በነገው ዕለት ማለትም ግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ስራ እንደሚመለሱ ተነግሯል፡፡
ይኸው አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ ከሚያዝያ ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን በሰራተኛ ማህበሩ በኩል የተጠየቀ ቢሆንም ድርጅቱ ባለመስማማቱ፣ የ 35 ከመቶ ጭማሪው ከግንቦት ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን ነው የተገለፀው፡፡
