“
ጠቅላይ ሚኒስትር ቢኒያም ኔታንያሁ “ፍልስጤማውያንን ለመቀበል ፍላጎት ያላቸውን ሀገራት እየፈለግን ነው” ብለዋል።
እስራኤል ወደጋዛ ለመግባት “ሙሉ ሃይሏን አዘጋጅታለች” ያሉት ኔታንያሁ “ሀማስን ሳናጠፋና ታጋቾችን ሳናስለቅቅ አንመለስም” ሲሉ ተናግረዋል።
“ሀማስ ታጋቾችን እለቃለሁ ሊል ይችላል፣ ጥሩ ነው ይመለሱ፣ እንቀበላለን ነገርግን ወደ ጋዛ መግባታችን የማይቀር ነው” ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ “ጦርነት ልናቆም የምንችልበት ሁኔታ አይኖርም” ያሉ ሲሆን “ጊዚያዊ የተኩስ አቁም ግን ሊኖር እንደሚችል ጠቁመዋል። #thenational
