ለቅርስ ጥበቃና ምርምር የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም

Date:

የቅርስ ጥበቃና የምርምር ዘርፍ ውስጥ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስፈላጊ ነው አሉ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው፡፡

ባለሥልጣኑ “የኢትዮጵያ ቅርስ ምርምር በዲጂታል ዘመን” በሚል መሪ ሃሳብ 3ኛውን ዓመታዊ የኢትዮጵያ ቅርስ ምርምር ጉባዔ እያካሄደ ነው፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ በኢትዮጵያ የሚገኙ ቅርሶችን ምዝገባ የሚያሳልጥ ሀገራዊ የመረጃ ቋት ለምቶ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡

የቅርስ ጥበቃና የምርምር ዘርፍ ውስጥ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው ÷ ባለስልጣኑ ዲጂታል አሰራርን እየተገበረ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ሀገሪቱ ከጀመረችው ‘ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030’ ስትራቴጂ ጋር በማጣጣም የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከየካቲት 2025 ጀምሮ ትልቅ የዲጂታላይዜሽን ሥራ ጀምሯል ነው ያሉት።

ተቋሙ በ2027 ዓ.ም የተወሰኑ አገልግሎቶችን፤ በ2030 ደግሞ ከቅርስ ጋር የተያያዙ አጠቃላይ አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ ዲጂታል ለማድረግ አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡

የሙዚዬም አገልግሎትን ዲጂታላይዝ በማድረግ በተሻለ ሁኔታ ለማስተዋወቅና የጎብኝዎችን እርካታ ለማሳደግ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

የቱሪዝም ሚኒስትር ዴዔታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) በበኩላቸው÷ ቅርሶችን ለመጠበቅ፣ ለማልማትና ለትውልድ ለማስተላለፍ የተጠበቀና የተደራጀ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በቤ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...