የበጀቱ አነስተኛ መሆን ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ችግር እንደፈጠረ ነው የተነገረው
በኢፌዴሪ ቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የጥናት ዳይሬከተር የሆኑት አቶ አንመው ታደሰ እንደተናገሩት ለሌሎች የትምህርት ተቋማት ከሚመደበው በጀት አንጻር ለቴከኒክ እና ሙያ ዘርፉ የሚመደበው በጀት አነስተኛ ነው::
ለዘርፉ አምስት በመቶ ብቻ የበጀት ድጋፍ ይደረግለታል። በዚህ በጀት ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ተግዳሮት ሆኗል ሲሉ መናገራቸው ኢፕድ ዘግቧል ::
