ለኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል የልብ ህክምና መሳሪያ ተበረከተ

Date:

ለኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል  በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነና ለበርካታ ህፃናት የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል የተባለ የልብ ህክምና መሳሪያ ተበረከተ::

የልብ ቀዶ ህክምናን ጨምሮ ሁሉንም የልብ ህክምናዎች በነፃ የሚሰጠው የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል አገልግሎቶችን የሚሰጠው ከሚሰበስበው እርዳታ ከሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት በሚደረግለት ድጋፍ መሆኑን ተናግሯል፡፡

ማዕከሉ የህክምና መሣሪያ ድጋፉን ያገኘው ላይፍ ፎር አፍሪካ ከተባለ የበጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን የልብ ህክምና መሳሪያው ለማዕከሉ የመጀመሪያ የሆነና ለበርካታ ህፃናትን በቀዶ ህክምና ጊዜ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል እንደሆነ ተነግሯል፡፡

የተደረገው የህክምና መሳሪያ ድጋፍ የልብ ቀዶ ህክምናው ከተከወነ በኋላ ልብ ሳይዘጋ ምን ያህል ለውጥ መጥቷል የሚለውን ለማየት የሚያግዝና ቀዶ ህክምናው ሳይጠናቀቅ ችግር ካለ ለመለየት የሚረዳ  በመሆኑ ተደጋጋሚ ቀዶ ህክምና እንዳይደረግና ስራውንም የሚጠይቀውንም ወጪንም የሚቆጥብ ነው ተብሏል፡፡

ላለፉት 7 ዓመታት ማህበራዊ ሚዲያ ለሰብዓዊነት በመጠቀም ማዕከሉን ስትረዳ በቆየችው በጎ አድራጊ ጋዜጠኛ ህይወት ታደሰ በተመሠረተው ላይፍ ፎር አፍሪካ  ተቋም የህክምና መሳሪያው መለገሱ ተነግሯል፡፡

የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል በኢትዮጵያ ብቸኛ የሆነና የነጻ የልብ ህክምና የሚሰጥ ማዕከል ሲሆን ማእከሉ ከመንግስት ምንም አይነት በጀት የማይመደበለትና ከተለያዩ ተቋማትና በጎ ፈቃደኞች በሚያገኘው ድጋፍ የሚንቀሳቀስ ነው ተብሏል፡፡

በተለይም ስራውን ለማስፋፋት በቂ የልብ ቀዶ ህክምና ባለሙያዎች ቢኖሩትም የግብዓት እጥረት ግን ትልቅ ፈተና እንደሆነበት ተነግሯ፡፡

በአሁኑ ሰአትም በማዕከሉ ከሰባት ሺ በላይ ሰዎች የልብ ህክምና ወረፋ በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን ሰምተናል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...