ፖርት ሱዳን-የሱዳን ጦርነት አካባቢዉን እያዳረሰ ነዉ

Date:

የሱዳን መከላከያ ጦር የሊቢያ የጦር አበጋዝ ኸሊፋ ሐፍጣር የሚያዙት ሚሊሺያ ጦር ጥቃት እንደከፈተበት አስታወቀ።

የሱዳን መከለከያ ጦር አዛዦች እንደሚሉት ሱዳንን ከሊቢያና ከግብፅ ጋር በሚያዋስነዉ ድንበር ላይ የሠፈረዉ ጦራቸዉ በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦርና በኸሊፋ ሐፍጣር ኃይላት የተቀናጀ ጥቃት ተከፍቶበታል።

ሶስት ማዕዘናማዉ አካባቢ ሠፍሮ የነበረዉ የሱዳን መከላከያ ጦር ዳግም ለመደራጀት ከአካባቢዉ ማፈግፈጉን አዛዦቹ አስታዉቀዋል።

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ለረጅም ጊዜ ከከበባት ከአል ፋሻር ከተማ በመቶዎች ኪሎ ሜትር  ርቀት ላይ በሚገኘዉ ድንበር ሠፍሮ የነበረዉ ጦር በአብዛኛዉ ከቀድሞ አማፂ ኃይላት ተዋጊዎች የተዉጣጣ ነዉ።

የሐፍጣርና የፈጥኖ ደራሹ ኃይላት የድንበሩን መተላለፊያ፣ ጦር መሳሪያ ለማሻገር ይጠቀሙበታል በማለትም የሱዳን መከላከያ ጦር ይወቅሳል የሐፍጣር ኃይል ግን ወቀሳዉን አስተባብሏል።

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ራሳቸዉን ፊልድ ማርሻል ብለዉ ለሚጠሩት ኸሊፋ ሐፍጣር ከፍተኛ ድጋፍ ከሚሰጡ መንግሥታት አንዷ ናት።

የሱዳን መከላከያ ጦር ደግሞ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦርን ትረዳለች በማለት በተደጋጋሚ ይወቅሳል።

dw amharic

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...