ለኢትዮጵያ የትምህርት መውደቅ ምክንያቱ ምንድነው ነው?

Date:

በዘርፉ ባለሞያዎች ለዚህ ችግር ምክንያት የተባሉ ነጥቦች ተዘርዝረው ሲቀርቡ ይሰማል፡፡

በትምህርት ዙሪያ የሚሰራ ተቋም አጠናሁት ብሎ ይፋ ባደረገው ውጤት የኢትዮጵያ የት/ት ሥርዓት ተማሪ የተሳሳተውን እንዲያውቅና መልሶ እንዲያርም እድል አለመስጠቱ ትልቁ ችግር ነው ብሏል፡፡

ተማሪዎች በፈተናዎች ወቅት የሚያገኙትን የተሳሳቱ መልሶቻቸውን እንዲያርሙ እድል አለመስጠታቸው እንደ ዋና ችግር ተመልክቼዋለሁ ያለው በዘርፉ ለ20 ዓመታት ሲሰራ የቆየው ዕርግብ የትምህርት አገልግሎት ይህም የስራ አጥ ቁጥር እንዲጨምር አድርጓል፣ ተማሪዎች ከሌሎች የአለም ሀገራት ጋር ተወዳዳሪነታቸው ዝቅተኛ እንዲሆን እና ሌሎች ችግሮችን አስከትሎብናል ብሏል።

በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ በአማካይ በዓመት ከ700 ሚሊዮን እስከ 1 ቢሊየን ኤክስ ለተማሪዎች እንደሚሰጥ ተመልክተናል ያሉት ዕርግብ የትምህርት አገልግሎት የእቅድ አስተዳደር ሀለፊ አቶ መርሃዊ ጎሹ አበበ አንድ አስተማሪም በዓመት እስከ 20,000  ኤክሶች ለተማሪዎች ይሰጣል ብለውናል፡፡
ለትምህርት ሥርዓቱ ዋነኛው ችግር ስህተትን አለማረም ሆኖ አግኝቸዋለሁ ያለው ድርጅቱ ይህ ችግር ደግሞ አሁን ላለንበት የትምህርት ምስቅልቅል ዳርጎናል ብሏል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. https://www.mixcloud.com/ShegerFM/63e-rtd/

ከሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...