ብሪክስ ፀረ-አሜሪካዊ እና በአሜሪካ ላይ ያነጣጠረ አለመሆኑን የሩሲያው ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ሪያብኮቭ ተናግረዋል።
አክለውም ነገሮችን ማመቻመች እንዲሚያስፈልግ ያሳወቁ ሲሆን የበላይነትን ማሳየት ከቡድኑ አባላት ጋር ለመነጋገር ጥሩ መንገድ አለመሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
👉 ቀደም ሲል ፕሬዝዳንት ትራምፕ ብሪክስን የሚደግፉ ሀገሮች ላይ 10 በመቶ ቀረጥ እጥላለሁ በማለት ማስፈራራታቸው ይታወሳል።
