116ኛውን የኢትዮጵያ ፖሊስ ምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች !!
ሚያዝያ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ በሚደረጉ የተለያዩ ወታደራዊ ትርዒቶች መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ ።፡፡
በዚህም መሠረት፦
ከ22 አደባባይ ወደ ወደ ቅዱስ ዑራኤል -መስቀል አደባባይ (22 አደባባይ በተመሣሣይ ዘሪሁን ህንፃ መስቀለኛ ላይ )
ከአትላስ መብራት ወደ ቅዱስ ዑራኤል አደባባይ (አትላስ መብራት እና ፒኮኪ መብራት ላይ)
ከቦሌ ወሎ ሠፈር መታጠፊያ ወደ ኦሎምፒያ አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)
ከወሎ ሠፈር ጀምሮ እስከ ጋዜቦ አደባባይ ውስጥ ውስጡን ወደ ዋናው መንገድ የሚያስወጡት
ከመስቀል ፍላዎር አደባባይ ወደ ጋዜቦ አደባባይ (መስቀል ፍላዎር አደባባይ ላይ )
ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ኤግዚብሽን ውስጥ ለውስጥ ወደ ፊላሚንጎ (ጋዜቦ አደባባይ ላይ )
ከቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክርሰቲያን ወደ ለገሃር መብራት ( ቅዱስ ቂርቆስ ወደ ጋዜቦ ላይ )
ከአጎና መስቀለኛ ወደ ጥላሁን አደባባይ
ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሀር መብራት (ሜክሲኮ አደባባይ ላይ)
ከፓርላማ መብራት ወደ ውጭ ጉዳይ (ፓርላማ መብራት ላይ )
ከጥይት ቤት ወደ ቅዱስ ገብርኤል (ጥይት ቤት መታጠፊያ ላይ )
ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ (ሴቶች አደባባይ ላይ )
ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል (ሴቶች አደባባይ ላይ) ከንጋቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ዝግ ይሆናሉ።
በተጨማሪም፦ ከቅዱስ ዑራኤል ወደ መስቀል አደባባይ
ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ
ከጥላሁን አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ
ከለገሃር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ
ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከብሔራዊ ቤተ መንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ ከዛሬ ማለትም ከ25/08/2017 ዓ/ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ ዝግ ሲሆን እንዲሁም ለዚሁ ፕሮግራም ሲባል ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ በመስመሮቹ ላይ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አሳስቧል።
