የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)ን በባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት ሾመዋል።
ፕሬዝደንቱ በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 71 ንዑስ አንቀጽ 3 መሰረት ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር)ን ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር አድርገው መሾማቸው ኢዜአ ዘግቧል።
አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ሆነው ሲሰሩ መቆየታቸው ይታወቃል።
ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በአምባሳደርነት መሾማቸውን ተከትሎ፤ ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን ሚኒስትርነታቸው ተነስተው በቦታቸው ሌላ ሚኒስትር እንደሚተካ ይጠበቃል፡፡
