ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለ 125ሺ ወጣቶች የዲጂታል ስልጠና እድል አመቻቸ

Date:

ዲጂታል ስልጠናው ቴክስታርት (Techstart) የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን ዛሬ ይፋ የተደረገ ነው፡፡

ስልጠናው በኢንተርኔት አማካይነት በኦንላይን የሚሰጥ ሲሆን በመጭዎቹ 3 ዓመታት ውስጥ የሚጠናቀቅ መሆኑን በላከልን መግለጫ ተናግሯል፡፡

እንድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆናቸው ወጣቶችን በአማዞን ድረ ገፅ የክህሎት ማዕከል መሰረታዊ የክላወድ ስልጠና እንዲያገኙ ቀጣይነት ያለው የድረ ገፅ አገልግሎት የዲጂታል ስልጠናም አመቻችቻለሁ ብሏል፡፡

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ይህን የማደርገው ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች በመደገፍ ቴክኖሎጂ መር የኢኮኖሚ ግቦችን እውን እንዲሆኑ ማህበራዊ ሀላፊነቴን ለመወጣት ነው ብሏል፡፡

በቅርቡ የተመሰረተው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ፋውንዴሸን ስልጠናውን በከፍተኛ ውጤት አጠናቅቀው አለም አቀፍ ተቀባይነት ያላቸው የምስክር ወረቀቶችን መውሰድ ለሚፈልጉ ሰልጣኞችም የመፈተኛ ክፍያዎች እንዲከፍሉላቸው ያመቻቻል ተብሏል፡፡

የፕሮግራሙን ይፋ መሆን አስመልክቶ የኩባንያው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ዊምቫን ሄሌፑት አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስልጠና ወደ ኢትዮጵያ ያመጣነው የቴክኖሎጂ ኮከቦችን ለማፍራትም በማለም ነው ብለዋል፡፡

የዲጂታል ስልጠና ምዝገባው በቅርቡ ይጀመራል የተባለ ሲሆን ለስልጠናው ብቁ የሚያደርጉ መስፈርቶች በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ማህበራዊ ትስስር ገጾች ይፋ ይደረጋል ተብሏል፡፡

ሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...