የአሜሪካ የጦር ሚኒስቴር ዋሽንግተን ለጦርነት መዘጋጀት እንዳለባት አሳሰበ።
የአሜሪካው መከላከያ ሚኒስትር ፔት ሀግሰት ለከፍተኛ የጦር ሀላፊዎች እና አዛዦች መልዕክት አስተላልፈዋል ።
ዋሽንግተን በአስቸኳይ በጦርነት መንፈስ ውስጥ መግባት እንዳለባት ያስገነዘቡት ሀግሰት አገራቸውን ምን ስጋት እንዳለባት ግን ይፋ አላደረጉም።
ፔንታጎን በቅርቡ ሁለት ወሳኝ የፖሊሲ ማሻሻያ ማድረጉንም ዘገባው አስታውሷል።
የብሄራዊ መከላከያ ስልቱን ከቻይና ወደ የውስጥ ደህንነት እና ምዕራቡ ንፍቀ ክበብ ማዞር አንደኛው ውጥኑ ሆኗል የአሜሪካ ጦር።
“ሰላምን ለማረጋገጥ ለጦርነት መዘጋጀት ይጠበቅብናል ” ብለዋል ፔት ሀግሰት።
በመቶዎች ለሚቆጠሩ የጦር አዛዦች በቨርጂኒያ የተናገሩት መከላከያ ሚኒስትሩ ውጥረት አሜሪካ እንዳለባትም አስጠንቅቀዋል።
ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካውን መከላከያ ሚኒስቴር ወደ ጦር ሚኒስቴር መለወጣቸው የዚህ ዓይነቱ ዝግጅት እንዳለ አመላካች ነው።
ዋይትሐውስ ለ2026 የመከላከያ በጀት 1.01 ትሪሊዮን ዶላር እንዲሆን መጠየቁም ይታወሳል።
ቀደም ሲል ከነበረው በጀት የ13.4 በመቶ ብልጫ ይኖረዋልም። ዘገባው የአር ቲ ነው
