ሊባኖስ በእስራኤል ጦር ተመታች

Date:

እስራኤል በበርካታ የሊባኖስ አካባቢዎች ላይ ከባድ የአየር ጥቃት ሰነዘረች።

የእስራኤል አየር ሀይል  በመላ ሊባኖስ ጥቃት ማደረሱን ከቤይሩት የሚወጡ መረጃዎች ያሳያሉ።

ተዋጊ ጀቶቹ በቦዳኢ ከተማ በምስራቃዊ ሊባኖስ  ቢያንስ ሶስት ጥቃት ማድረሳቸው ተነግሯል።

ከባዓ’ልቤክ ባሻገር ተጨማሪ ሶስት ጥቃቶች በአርዚ እና ቡርጅ ራሃል ከተሞች በደቡባዊ ሊባኖስ ደርሰዋል፡፡

በሊታኒ ወንዝ እና በሌሎች በርካታ የደቡባዊ ሊባኖስ ክፍሎች ከባድ የአየር ጥቃት መፈጸሙን የቤይሩት ምንጮች አረጋግጠዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከጋዛ ወደ እስራኤል ሮኬት መወንጨፉ ተሰምቷል።

የእስራኤል ጦር ሮኬቱ በኪቡትዝ አቅራቢያ መውደቁን አረጋግጣል፡፡

የሃማስ ክንፍ  ቃሳም ብርጌድ በራጁም ሮኬቶች እስራኤል ላይ ጥቃት አድርሻለሁ ብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ውጭ ምንዛሪ የሚያድኑ የሴራሚክ ምርቶች በቅርቡ ለገበያ ይቀርባሉ

ይህ የተገለፀው ኢትዮደር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በ”Golden Tier...

የዓለም የቡና ገበያ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ተገለጠ

በዓለም አቀፍ ደረጃ በቡና አቅርቦት ላይ ተፈጥሮ የነበረው ስጋት...

አሜሪካ የኢራንን የጭነት መርከብን መያዟን አስታወቀች

በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን የዘጋችው...