ሌ/ጄነራል ታደሰ አዲስ አበባ ገቡ !

Date:

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ቀጣይ እጣ ፈንታ ምን ይሆን?

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ፣ በክልሉ ወቅታዊና አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ዛሬ እሁድ መጋቢት 27 ቀን 2018 ዓ.ም አመሻሽ ላይ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ጄነራሉ በቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ከከፍተኛ የፌደራል ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተው እንደሚመክሩ የተገለጸ ሲሆን፣ ጉብኝቱ በትግራይ ክልል ባለው የጸጥታና የፖለቲካ ሁኔታ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ምንጮች ጠቁመዋል።

ይህ ጉዞ ትልቅ ትኩረት የሳበው ጄነራል ታደሰ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ተሰጥቷቸው የነበረው የአንድ ዓመት የሥልጣን ጊዜ ከሦስት ቀናት በኋላ (መጋቢት 30) ስለሚያበቃ ነው።

ጄነራሉ ለተጨማሪ ስድስት ወራት በሥልጣን ላይ ይቆያሉ ወይስ አዲስ ምትክ ይመደባል የሚለው ጥያቄ በብዙዎች ዘንድ አነጋጋሪ ሆኗል። የአዲስ አበባው ውይይትም የጊዜያዊ አስተዳደሩን ቀጣይ እጣ ፈንታና የክልሉን የሽግግር ሂደት የሚወስን ወሳኝ ክስተት እንደሚሆን ይጠበቃል።

አውራምባ ታይምስ –

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...