መርስክ የበርበራ ወደብ የጭነት አገልግሎቶችን ለጊዜው አቋረጠ

Date:

የዓለማችን ግዙፍ የመርከብ ድርጅት የሆነው መርስክ ፣ ወደ በርበራ ወደብ የሚደረጉ እና ከወደቡ የሚወጡ አዳዲስ የጭነት ቦታ ማስያዣዎችን ለጊዜው ማቋረጡን በይፋ አስታውቋል።

ኩባንያው ለዚህ አስቸኳይ ውሳኔ ምክንያት የሆነው በመርከብ የጉዞ መርሃ ግብር ላይ የተደረገ ለውጥ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ይህም ውሳኔ በተለይ በርበራን እንደ አማራጭ የንግድ በር ለምትጠቀመው ኢትዮጵያ ከፍተኛ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይገመታል።

በቅርብ ዓመታት የበርበራ ወደብ ለኢትዮጵያ ወሳኝ የሆኑ እንደ ማዳበሪያና እህል ያሉ ምርቶችን ለማስገባት ትልቅ ሚና እየተጫወተ የሚገኝ በመሆኑ፣ የአገልግሎቱ መቋረጥ በቀጠናው የንግድ እንቅስቃሴ ላይ የራሱ ጥላ ማረፉ አይቀሬ ነው።

መርስክ አዳዲስ የጭነት ጥያቄዎችን መቀበል ቢያቆምም፣ ቀደም ብለው የተጫኑ እና በጉዞ ላይ ያሉ ንብረቶች በታቀደው መሠረት መድረሻቸው እንዲገቡ እንደሚያደርግ አረጋግጧል።

በተጨማሪም ድርጅቱ ደንበኞቹ የአቅርቦት ሰንሰለታቸው እንዳይስተጓጎል አሁንም አገልግሎት እየሰጡ ያሉትን የጅቡቲ፣ የሞቃዲሾ እና የሞምባሳ ወደቦችን እንደ አማራጭ እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...