ማሊ ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት እንዳላቸዉ ደርሼበታለሁ ያለቻቸዉን ከ80 በላይ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ወሰደች።
በወታደራዊ መንግስት የምትመራዋ ማሊ፤ በማዕከላዊና ምዕራባዊ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ በፈጸመችዉ ጥቃት ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት አላቸዉ ያለቻቸዉን ከ80 በላይ ታጣቂዎችን መግደሏን የጦር ኃይሏገልጿል፡፡
የጦር ኃይሉ በብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጠው መግለጫ፤እርምጃዉ የተወሰደዉ በሰባት ከተሞች ላይ መሆኑን ገልጾ፤ በሴኔጋል ደግሞ ከሞሪታኒያ ጋር በሚዋሰኑበት ድንበር ጥቃቶቹ እንደተፈፀሙ ተናግረዋል፡፡
የታጣቂ ሀይሉ በበኩሉ በተቀናጀ መልኩ ጥቃት መፈፀሙን ገልጾ፤ሶስት የመንግስት ወታደራዊ ካምፖችን መቆጣጠሩን አስታዉቋል፡፡
የማሊ መንግስት በማሊ የተለያዩ አካባቢዎች ለ30 ቀናት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አዉጇል።
በአፍሪካ የአሜሪካ ዕዝ (አፍሪኮም) ማሊ፣ ቡርኪናፋሶ እና ኒጀርን የያዘው የሳህል ቀጣና የዓለም የሽብር ማዕከል ነው ሲል ገልጾታል።
የሽብር ቡድኖቹም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና በኮንትሮባንድ የጦር መሳሪያ ንግድ ገቢያቸውን በከፍተኛ ደረጃ እያሳደጉ ይገኛሉ ሲል አፍሪካኒውስ ዘግቧል።
ማሊ ከፈረንጆቹ 2020 ጀምሮ በወታደራዊ ሃይል እየተመራች መሆኑ ይታወቃል፡፡
